Monday, September 2, 2013

የዘመን አቆጣጠር ባሕረ ሐሳብ

               Source:Dn. Melaku Ezezew
1. ባሕረ ሐሳብ ማለት ምን ማለት ነው?

ባሕረ ሐሳብ ማለት ቁጥር ያለው ዘመን ማለት ነው፡፡ በሌላ አገላለጽም የሐሳብባሕር ማለት ነው፡፡ በዓላት እና አጽዋማትን ለማውጣት የመደመር፣ የመቀነስ፣የማባዛት ስሌትን ብቻ ሳይሆን ሐሳበ ፀሐይን፣ ሐሳበ ወርኅን፣ ሐሳበ ከዋክብትን ሐሳበዐበቅቴን ወዘተ አጠቃሎ የያዘ እንደ ባሕር የሰፋ በመሆኑ የሐሳብ ባሕር ተብሏል፡፡የዘመን አቈጣጠር ማለት ስለማሕበራዊ ኑሮ ጠቄሜታና የሃይማኖት ተግባሮችለማከናወን በሚያገለግል መልኩ ተፈጥሮአዊውን የወቅቶች ክፍፍል እርስ በርሳቸውየማመቻቸት ዘዴ ነው፡፡
ማርቆስ ወንጌላዊ

ሐሳበ ዘመን የዘመን አቆጣጠርማለት ሲሆን የሐሳበ ዘመን ትምህርትባሕረ ሐሳብ ይባላል፡፡ ባሕረ ሐሳብየሚለው ቃል ሐሰበ ቆጠረ ከሚለው ግስየወጣ ዘመድ ዘር ነው፡፡ ስለዚህ ባሕረሐሳብ ማለት ቁጥር ያለው ዘመን ወይምዓመተ ዓለም ማለት ነው፡፡ ባሕረሐሳብ መባሉም የባሕር አዝዋሪቱ፣መንገዱን፣ ጥልቀቱና ስፋቱ ረዥምናሰፊ እንደሆነ የባሕረ ሐሳብ ትምህርትምመንገዱን ስፋቱ ልዩ ልዩ በሆነየአጽዋማትና የሱባዔያት ምሥጢርየተሰናዳ ስለሆነ ነው፡፡

«ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ»

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
ነሐሴ 15/2003 ዓ.ም
Emebetachin-Erigetፆመ ፍልሰታ የእመቤታችን ዕረፍት፣ ትንሣኤና ዕርገቷ የሚታሰብበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ወቅት ምእመናንን ከአካባቢያቸው ራቅ ብለው በተለያዩ ገዳማትና አድባራት በመሄድ አሊያም በአጥቢያቸው በመሰባሰብ እመቤታችን ለሐዋርያት በተለያዩ ጊዜያት ተገልጻ ሞትና ትንሣኤዋን የገለጸችበትን ሁኔታ ያስባሉ፡፡ ጌታም እናቱን መንበር አድርጎ ቀድሶ ማቁረቡን ይዘክራሉ በዚህ ወቅት በፆም በጸሎት ተወስነው የልጇን ቸርነት የድንግልን አማላጅነት ይማጸናሉ፡፡ ሁሉም እንደሚደረግላቸው ያምናሉ፡፡ የሱባኤው ወቅት ሲፈጸም «በእውነት ተነሥታለች» ብለው በደስታ የፆሙን ወቅት ይፈጽማሉ፡፡

 
ሞትና ትንሣኤዋ እንዴት ነው ቢሉ፡-
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ ነገረ ማርያም፣ ስንክሳር እና ተኣምረ ማርያም እንደሚያስረዱት፤ ጥር 21 ቀን ዐርፋለች፡፡ ሞቷ የሚያስደንቅ መሆኑን ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ያሬድ  «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የሐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል፡፡

Sunday, January 20, 2013

በትክክል ያልመለስኳቸው ጥያቄዎች




1.    እግዚአብሔር ትወደዋለህ ? አዎ?
እግዚአብሔርን ትወደዋለህ ብለው ሲጠይቁት በልብ  ሙሉነት አዎ እግዚአብሔርን እወደዋለሁ ብየ ከመለስኩ በሗላ ጥያቄውን እራሴን ደግሜ ብጠይቀው። አዎ ብሎ ለመመለስ የሚያስችል ድፍረት እንደሌለኝ ውስጤ ነገረኝ።እግዚአብሔርን ብወደውማ ኑሮ፦
-     የእርሱን ህግጋት በአከበርኩ ነበር
-     ከራሴ ፈቃድ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በአስቀደምኩ ነበር
-     ጠላቶቼን በወደደኩ፣የራሴን የባንክ አካውንት ከፍ ለማድረግ ከመታገል ይልቅ የተራቡትን ለማብላት የታረዙትን ለማስበስ በተጋሁ ነበር።
-     በክርስቶስ አምሳል የተሰራው ወንድሜ (እህቴ) በረሃብና ቁር እየተሰቃየ በተዋቡ አልጋዎች ባልተኛሁ ነበር።……አረ ስንቱ!